Adam Reta – አዳም ረታ – የአዳም ሥራዎች
ይፋዊ ድረ-ገጽ · adamretabooks.et
ዋና ሥራዎቹ
ማሕሌት
ግራጭ ቃጭሎች
መረቅ
Addis Ababa Noir
ደራሲው
አዳም ረታ ከ 1970ዎቹ ጀምሮ አጫጭር ልብ ወለዶችን፣ ግጥሞችና የረዥም ልብ ወለድ ድርሰቶች መፃፍ ጀምሯል። “ማሕሌት” በ 1981 ከታተመ ወዲህ ለኢትዮጵያ ሥነ-ጽሑፍ ቀዳሚ ድምጽ ሆኗል።
ሥነ-ጽሑፋዊ ፍልስፍናው ከአገራችን አንኳር ቁሳቁስ ይፈልቃል — ከእንጀራ፣ ከጉርሻ፣ ከልቃቂት፣ ከአደይ አበባ — አገሬው የሚኖረውን ዕለታዊ ሕይወት ቀምሮ በሥነ-ጽሑፍ አቅርቦታል።
አስተያየቶች
ከዘመናዊ አጭር ልብ ወለድ… የአዳም ረታን ማሕሌት እወዳለሁ። የኢትዮጵያውያንን ልብ አውቄበታለሁ።
[አዳም] ከአገረሰባዊ እሴቶች — ከእንጀራ፣ ከጉርሻ፣ ከልቃቂት ቅርፅ ወስዶ ተናጥላዊ ኢትዮጵያዊ ንፅረተ ዓለምን ለመቅረፅ ደፍሯል።
እንደ ተወርዋሪ ኮከብ የብርሀን ፈለጉን ከኋላው እየተወ በትውልዶች ሕዋ ላይ ለረጅም ዘመን የሚታይ ደራሲ አዳም ረታ ብቻ ነው።
አዳምን ያላየ ምንጭ ያመሰግናል።